በስደተኞች ማጎርያ ቤት ላይ በተነሳ የእሳት ቃጠሎ በርካቶች ስደተኞች ለሞት ተዳረጉ

Read a text description of this video
Transcript

አብዛኞቹ የኢትዮጵያ ዜጎች የሆኑ እና በስደተኛ ማጎሪያዎች ለረሀብ የተዳረጉ  በየመን፣ ሰነዓ የፓስፖርት እና የዜግነትጉዳይ ባለስልጣን የታገቱ ስደተኞች። የካቲት 28 ቀን 2013 ዓ.ም ስደተኞቹ የታጎሩበት ጣቢያ አሰቃቂ ሁኔታ እና ያለአንዳች ወንጀል (ክስ) መታሰራቸውን በመቃወም የረሀብ አድማ አደረጉ። በዚህ ወቅት የማጎሪያ ጣቢያው ጠባቂዎችከስደተኞቹ ጋር ሰጣ ገባ ውስጥ ከገቡ በኋላ ሁሉንም ስደተኞች በማጎርያ ክፍሎች ካስገቧቸው በኋላ ምግብናመጠጥ ከለከሏቸው። ከዝያም ጠባቂዎቹ ከአካባቢው ለደቂቃዎች ከተሰወሩ በኋላ ሙሉ የጦር መሳርያ የታጠቁየሁቲ የጸጥታ ሀይሎች ጋር ተመልሰው መጡ። ከመካከላቸው አንደኛው የጥበቃ አባል ክፍት ስፍራ ካለው ጣርያውላይ በመውጣት ሁለት ተቀጣጣይ ፈንጂዎችን ስደተኞቹ ወዳሉበት ክፍል ወረወረ። በመጀመርያ የወረወረውከፍተኛ ጪስ በመፍጠር የስደተኞቹ አይኖች በእንባ እንዲሞሉ እና ማየት እንዳይችሉ አደረገ። ሁለተኛ የተወረወረውፈንጂ ደግሞ የእሳት ቃጠሎ አስነሳ። በግምት ከ10 እስከ 15 ደቂቃ ቆይታ በኋላ ከውጭ የነበሩ ሌሎች ሰዎችየስደተኞቹን ክፍሎች ግድግዳና በሮች በማፍረስ የተወሰኑ ስደተኞችን ህይወት ሲያተርፉ በርካቶች ግን በአስከፊሁኔታ ሞተዋል።

በየመን፣ ሰነዓ የካቲት 28 ቀን 2013 በርካታ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በእሳት ተቃጥለው የሞቱበትን የስደተኞች ማጎሪያጣቢያ በእሳት ሲቃጠልና ስደተኞቹ በድንጋጤና በጭንቀት ውስጥ ሆነው ሲመለከቱ። 

Region / Country